2023-04-29 16:34:18
ከ258 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመቱ የኮንትሮባንድ እቃዎች ተያዙ
አዲስ አበባ ፣ ሚያዝያ 21 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የጉምሩክ ኮሚሽን ከሚያዚያ 13 ቀን እስከ 19 /2015 ዓ.ም ባደረገው ክትትል ከ258 ሚሊየን ብር በላይ ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ እቃዎች ተይዘዋል፡፡
ኮሚሽኑ እንደገለጸው ÷ 214 ነጥብ 4 ሚሊየን የገቢ የኮንትሮባንድ እቃዎች እና 43 ነጥብ 6 ሚሊየን ብር የወጭኮንትሮባንድ ዕቃዎች ፤ በድምሩ ከ258 ነጥብ 1 ሚሊየን ብር በላይ የሚያወጡ የኮንትሮባንድ እቃዎች ናቸው በተለያዩ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች የተያዙት ፡፡
በቁጥጥር ስር ከዋሉት የኮንትሮባንድ እቃዎች መካከል አልባሳት፣ ነዳጅ፣ የቁም እንስሳት፣ ኤሌክትሮኒክስ፣ ቡና፣ መድሀኒት፣ ተሽከርካሪዎች፣ የመዋቢያ እቃዎች የጦር መሳሪያዎች፣ ጫት፣ አደንዛዥ እጾች፣የምግብ ዘይትና የተለያዩ ሀገር ገንዘቦች እነደሚገኙበት ተገልጿል፡፡
የኮንትሮባንድ ዕቃዎቹ የጉምሩክ ኮሚሽን ሰራተኞች፣ ፌደራል ፖሊስ፣ የክልል ፖሊስ አባላትና ህብረተሰቡ ባደረጉት የጋራ ጥረት መያዛቸውም ነው የተገለጸው፡፡
እቃዎቹን ሲያዘዋዉሩ የተገኙ አስር ግለሰቦችና ሦስት ተሽከርካሪዎችም በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ከኮሚሽኑ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
ኮሚሽኑ በዚህ የህግ ማስከበር ስራ ላይ ለተሳተፉ አካላትም ህዝብ ምስጋና አቅርቧል፡፡
የኮንትሮባንድና ህገወጥ ንግድ የአፈጻጸም ስልቱ ተለዋዋጭ በመሆኑ ድርጊቱን ለመግታትና በሀገር ኢኮኖሚ የሚያሳድረውን አሉታዊ ተጽእኖ ለመከላከል ሁሉም ባላድርሻ አካላትና ህብረተሰቡ የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ ኮሚሽኑ ጥሪ አቅርቧል፡፡
217 views13:34